Warning: Undefined variable $currentLang in /var/www/html/news.php on line 27
Operation Rescue Ethiopia — African Children's Day — Adwa Provides Financial Support for Celebrations
Ethiopian children news
የቅርብ ዜናዎች

የአፍሪካ ሕፃናት ቀን — ለክስተቶቹ ድርጅቱ ድጋፍ ሰጥቷል

← የቅርብ ዜናዎች
📍 Adwa Branch Operation Rescue Ethiopia Adwa · June 15, 2025
የአፍሪካ ሕፃናት ቀን — ለክስተቶቹ ድርጅቱ ድጋፍ ሰጥቷል
በአፍሪካ ህፃናት ቀን አጋጣሚ ኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ ለዕለቱ ውሎ የሚያስፈልገውን ሙሉ የገንዘብና የዝግጅት ድጋፍ በማድረግ ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብሯል። ከማዕከላችን የተገኙ ህፃናት መልዕክት የያዙ ባነሮችን በመያዝ፣ የጋራ ፎቶዎችን በመነሳት እና በማህበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ በእያንዳንዱ የአፍሪካ ህፃን መብትና ክብር ላይ ያተኮሩ መርሃ-ግብሮችን አከናውነዋል። በኦፐሬሽን ሬስኪዩ እምነት፡ ማንኛውም ህፃን የቤተሰብ ወይም የማህበረሰብ ሁኔታው ምንም ይሁን ምን፡ ሊከበር፣ ሊጠበቅ እና መዋዕለ ነዋይ ሊፈሰስበት ይገባል የሚል ፅኑ አቋም አለን። የአፍሪካ ህፃናትን ቀን ማከበር ለእኛ መደበኛ የበዓል ኩነት ብቻ ሳይሆን፣ የህፃናትን መብት ለማስከበርና የነገውን መጻኢ እድላቸውን ለማቅናት ያለንን ቁርጠኝነት የምናድስበት ነው። ህፃናት ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ በትምህርት የበቁ እና ብሩህ አእምሮ ያላቸው ሆነው እንዲያድጉ ከአካባቢውና ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሰራለን።

ይለግሱ & ሕፃን ይደግፉ

በወር ከ50 ዶላር ($50) ጀምሮ አንድ ሕፃን ሙሉ እንክብካቤ ምግብ፣ ትምህርትና መጠለያ እንዲያገኝ ማድረግ ይቻላል።