በአፍሪካ ህፃናት ቀን አጋጣሚ ኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ ለዕለቱ ውሎ የሚያስፈልገውን ሙሉ የገንዘብና የዝግጅት ድጋፍ በማድረግ ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብሯል። ከማዕከላችን የተገኙ ህፃናት መልዕክት የያዙ ባነሮችን በመያዝ፣ የጋራ ፎቶዎችን በመነሳት እና በማህበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ በእያንዳንዱ የአፍሪካ ህፃን መብትና ክብር ላይ ያተኮሩ መርሃ-ግብሮችን አከናውነዋል።
በኦፐሬሽን ሬስኪዩ እምነት፡ ማንኛውም ህፃን የቤተሰብ ወይም የማህበረሰብ ሁኔታው ምንም ይሁን ምን፡ ሊከበር፣ ሊጠበቅ እና መዋዕለ ነዋይ ሊፈሰስበት ይገባል የሚል ፅኑ አቋም አለን። የአፍሪካ ህፃናትን ቀን ማከበር ለእኛ መደበኛ የበዓል ኩነት ብቻ ሳይሆን፣ የህፃናትን መብት ለማስከበርና የነገውን መጻኢ እድላቸውን ለማቅናት ያለንን ቁርጠኝነት የምናድስበት ነው። ህፃናት ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ በትምህርት የበቁ እና ብሩህ አእምሮ ያላቸው ሆነው እንዲያድጉ ከአካባቢውና ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘን እንሰራለን።