በዓድዋ ማዕከላችን በዓልን ምክንያት በማድረግ ልዩ የሰንበት/የበዓል የምሳ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ነበር። ህፃናቱ፣ ሰራተኞች እና አስተማሪዎቻቸው በአንድ ላይ በመሰብሰብ፡ በፍቅር በተዘጋጁ ጠረጴዛዎች ዙሪያ በመቀመጥ፣ ትኩስ ምግብ እና ጁስ እየተመገቡ የበዓሉን ደስታ በጋራ አሳልፈዋል።
በማዕከሉ ኩሽና ውስጥ በሰራተኞች እና በህፃናቱ ትብብር የሚጣፍጥ ወጥ በጋራ ሲሰራ የነበረው ጊዜ የፍቅርና የአንድነት ማሳያ ነበር። እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎች ኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ ከተራ ድርጅት በላይ እውነተኛ አፍቃሪ ቤተሰብ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው እያንዳንዱ ህፃን ትኩረት፣ እንክብካቤ እና የራሱ የሆነ አባትና እናት የሚመስል ቤተሰብ የሚያገኝበት ድንቅ ስፍራ ነው።