በኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ እኩል የትምህርት ዕድል ማግኘት ድህነትን በዘላቂነት ለማሸነፍ መሰረት መሆኑን አፅንኦት ሰጥተን እንምናለን። የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት የትምህርት ዘመን ሲጀመር ድርጅታችን ለ100 ወላጅ አልባ እና ተጋላጭ ህፃናት (OVC) ሙሉ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ይህንን ድጋፍ ሙሉ ለማድረግ እና ተማሪዎቹ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ እንዲሆኑ ለማስቻል በሚቀጥሉት ቀናት የትምህርት ቤት ዩኒፎርም ድጋፍ የምናደርግ ይሆናል።
ይህ ስራ ኦፐሬሽን ሬስኪዩ በትምህርት ላይ እንዴት መዋዕለ ነዋይ እንደሚያፈስ ማሳያ ነው የገንዘብ እንቅፋቶችን በማስወገድ ህፃናቱ አዘውትረው ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ እና ለጥናታቸው የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ በማሟላት። ለተማሪዎች ደብተር፣ እስክሪብቶ፣ ቦርሳ እና ዩኒፎርም ማቅረብ ከቁሳቁስ ድጋፍ ባለፈ ክብራቸውን የሚያስጠብቅ፣ በራሳቸው የመተማመን አቅማቸውን የሚያሳድግ እና ብሩህ ተስፋን የሚሰጥ ነው። እርስዎም በዚህ በነገው ትውልድ ላይ የምናደርገውን ታላቅ መዋዕለ ነዋይ በመደገፍ ከእኛ ጋር እንዲሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።