የማይጨው ፕሮጀክት፡ ኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ (ORE) ባለፉት 25 ዓመታት በመላው ትግራይ በገነባው ታላቅ እምነትና መልካም ስም እንዲሁም ከአካባቢው አስተዳደር በተደረገለት ድጋፍ በራሱ ህንፃ ስራውን በቀጥታ በመጀመሩ ልዩ ያደርገዋል። በአሁኑ ወቅት ሃምሳ (50) ህፃናት ተመዝግበው አገልግሎቱንና ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ።
የማይጨው ማህበረሰብ ኦኣርኢ በነመቀሌ፣ ዓዲግራት እና ዓድዋ ያሳየውን አዎንታዊ ስራ እና ያመጣውን በጎ ተፅዕኖ ከተመለከተ በኋላ ፕሮጀክቱን በሙሉ ደስታ እና በክፍት ክንድ ተቀብሎታል። የነዚህ ህፃናት መጻኢ ጊዜ በእርግጥም ብሩህ ነው።