የማይጨው ቅርንጫፍ ይፋዊ የምረቃ በዓል አካል በመሆን ለያንዳንዱ ተመዝጋቢ ቤተሰብ 50 ኪሎ ግራም ጤፍ ተከፋፍሏል። በመግቢያው ላይ የተሰቀለው ባነር "የኦፐሬሽን ሬስኪዩ ኢትዮጵያ በማይጨው የህፃናት እንክብካቤ ፕሮጀክት የምረቃ እና የከፈታ ሥነ-ሥርዓት" የሚል ጽሑፍ የያዘ ነበር።
የአካባቢው ባለስልጣናት፣ የድርጅቱ የቦርድ አባላት፣ ሰራተኞች እና ቤተሰቦች በጋራ በመሆን የአዲስ ጅምር እንዲሁም የብዙ ዓመታት ጸሎትና እቅድ ፍፃሜ የሆነበትን ድንቅ ቀን አክብረዋል። የማይጨው ህፃናት አሁን የራሳቸው የሆነ አስተማማኝ ቤት አግኝተዋል።